Image placeholder
በ2015 ዓ.ም የበጀት አመት በጉለሌ ክፍለ ከተማ ለህዳሴ ግድብ ግንባታ 55,280,292 ብር ተሰበሰበ፤
By Belay | 2023-08-04

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ታላቁ የህዳሴ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት ፅ/ቤት በ2015 ዓ.ም በጀት አመት ከ55 ሚሊዮን ብር በላይ በመሰብሰብ የእቅዱን 122% ማሳካቱን ጽ/ቤቱ አስታውቋል።

የጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት ጽ/ቤት በሃብት አሰባሰብ እና በህዝብ ንቅናቄ ተሳትፎ በኩል የነበረውን የ2015 ዓ.ም አፈፃፀም ከፍተኛ በመሆኑ የአ.አ ከተማ አስተዳደር የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት የላቀ አፈጻጸም የምስጋናና የእውቅና ዋንጫና ሰርተፍኬት አበርክቶልናል።

እውቅናውና የላቀ አስተዋጽኦ እንዲመጣ ላደረጉ የክ/ከተማና የወረዳ አስተባባሪ አካላት;አመራሩና መላው የክፍለ ከተማችን ነዋሪዎች ላቅ ያለ ምስጋና በማቅረብ በቀጣይም ድጋፉን አጠናክሮ እንዲቀጥል ተጠይቋል።

የቅርብ ዜና


Loading...